አምልኮ/Worship

ግን ምንድን ነው፣ ኀልዎቱ የመለኮቱ?

ከሰሎሞን ጥላሁን ፌስ ቡክ ገጽ የተገኘ ጽሁፍ

እግዚአብሔር ሳይከፋፈል ሳያንስና ሳይበዛ በፍጥረተ ዓለሙ ሁሉ በሙላቱ ይገኛል፣ ይህ ጠባዩ omnipresence/ “ክሳቴ ኩሉ” ይባላል። ድብልቅልቅ ባለው የመርካቶ ግፊያ መሃል ያለ አንድ ገበያተኛ በጠፈር ምርምር ማርስ ላይ የወጣ ጓደኛው ስልክ ደውሎ እግዚአብሔር በዚህ አለ ቢለው መርካቶ መሐል ካለው ማንነቱ የተሻለና ንጹህ ማንነት አለው ማለት አይደለም። እነዚህ የእኛ ርቀቶች ለእግዚአብሔር በኢንች አይራራቁበትም፣ ሥፍራዎች ሳይፈጠሩ በፊት የነበረው በስፍራዎች ሁሉ ሳይቀናነስ አለ- መገኛዎቹ ግን እርሱነቱ አይደሉም … በብሉይ ለምሳሌ ታቦቱን አስመልክቶ ሲስቱ፣ “ታቦቱን ይዘን ጦርነት ብንወጣ ድል እናደርጋለን” አሉ እነርሱም አለቁ ታቦቱም ተማረከ። የመገኛው ምሳሌና እርሱ ራሱን ሲያምታቱ ሳጥን ውስጥ እንደማይገባላቸው አሳያቸው! …ለምሳሌ በአዲስ ኪዳን አማኞች  ሲስቱ “የመለኮት ማደሪያ መለኮት ነን አሉ”፣ (አፌ ቁርጥ ይበል) ግማሾቹም ሞቱ ያሉትም አሉ በሙተት ላይ። ስለዚህ ከእኛ ጋር ነው እንጂ እኛን አይደለም!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!

ይህ ሳይርቅ መቅረቡ “አባታችን ሆይ” እንድንል ሲያደርገን፣ ረቂቅና ምጡቅነቱ (ትራንሴንደንስ) “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ” እንድንል ያደርገናል። ክርስትናን ልዩ የሚያደርገው ይህ ነው።  ስለዚህ እየቀረብነው እንፈራዋለን እየፈራነው እንወደዋለን!

የህልውናው ስሜት የመገኘቱ መገለጥ ነው እንጂ የሆነ ቦታ የሄደው ሲመጣ አይደለም፣ “እግዜር ” ለአፍታ በመሄዱ የተነሳ የሌለበት ቦታ ሊኖር አይችልም፣ እነዚህ ሁሉ መለዋወጦች ያሉት እኛ ዘንድ ነው። እኛ ከዚያ ስንመጣ ያለነው እዚህ ነው፣ ከዚህ ስንሄድ ያለነው እዚያ ነው! ለእግዜር ግን ህልውናው በመጠን አይቀናነስም። የእግዚአብሔር መገኘት እኛ ሲሰማን ከሆነ ቦታ መጣሁ ብሏቸው አደለም እኛ ዘንድ ያለው – ኢያኢሮስ ይሔ ስለገባው ነው ጌታን “ባትሔድም እዚያ ነህ ብቻ ቃል ተናገር” ያለው። እዚህ የእድሜ ልክ ደም ፍሳሽ ሲያቆም በዚያው ሰከንድ እዚያ ማዶ ከመቅሰፍት ሞት ይመልሳል! ሉቃስ 8:41-56 ስለዚህ እቅርብ ላለው ጉዳያችን ደሜን አቁምልኝ ስንለው ሩቅ ያለውን ጉዳያችንን ከሞት አስነሳልኝ የማለት የእምነት ድፍረት ይፈቀድልናል!

የእግዚአብሔር የህልውናው ተሰምቴዎቻችን መለዋወጥ እኛ ዘንድ ካሉ ልምምዶች ጋር የተያያዙ ናቸው። ምንም እንኳ የህልውናው ስሜት ለሁላችንም “እነሆ” የተባለ ቢሆንም፣ ሁላችንም አንድ ዓይነት ስላልሆንን በተመሳሳይ አንለማመደውም! እድሜ፣ ያለንበት መንፈሳዊ ደረጃ፣ የመንፈሳዊ የህይወት ተሞክሮ፣ የምንሰጠው ጊዜ “ሊትል ኢንቲሜሴ ሊትል ካፓሲቲ” አለ [ቶኒ ኤቫንስ] ልምምዶቻችን ይለያያሉ፣ ሁላችንም ግን መንፈሳችን ክፍት ነው … ለህልውናው መነካኪያ ቅባሪ የሰው ልጅ ሁሉ አለው። ስለዚህ በምንም ዓይነት መንፈሳዊ ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም የኅልውናውን ስሜት አለመፈለግ ከተፈጠርንበት አላማ በታች ለመኖር መወሰን ነው! እግዚኦ በሉ አንድ ጊዜ ፟_ ስንት ቀን ነው ያለዚህ ስሜት መኖር የምትችሉት? እነሆ ምርጫው የእናንተው ነው፣ አማኝ ሆኖ እንደ አላማኝ መኖር ….

እግዚአብሔር የህልውናውን ስሜት ከሌሎች የተሻለ ነጥሎ ለእገሌ አብዝቶ የሰጠው የለም “ኤልያስ እንደኛው ሰው ነበረ ..” ማለት ይኽው ነው…. እንዲያውም ብዙ ጊዜ ስፍራ የሚያናውጠው በማህበር ሲያገኘን ነው፤ የሐዋ 2፡… እነርሱም ስፍራውም ተናወጠ ዘጸ 40 … ተራራው ጤሰ – ስለዚህ ስንሰበሰብ ኅልውናው ይሰማናል ወይ? ስንሰባሰብ የማን ኅልውና ይሰማናል? ወንድሞች በኅብረት …
እግዚአብሔር እዚህ/እዛ ነው እንጂ እዚህ ብቻ እና እዛ ብቻ አይደለም። በክርስትና አስተምህሮ ሁለት የእግዚአብሔር ሀልዎት መገለጫ ቃሎች አሉ መለኮታዊ ምጡቅነቱና መለኮራዊ ቅርበቱ (138 ፡7)…  እግዚአብሔር ሳያንስና ሳይበዛ ያለ መስፈሪያ አለ።

ሀ. ወደ ላይና ወደ ታች 7- 8 የምታወቀው በምድር ላይ ስላለሁ ነው ብዩ ወደ ሰማይ ብመጥቅ ቀድመኸኝ አገኝሃለሁ ወደ ታችኛው ጥልቁ ብሔድ የዚህም ሥፍራ ዳኛ አንተ ሆነህ አገኝሃለሁ (አሞጽ 9:2)
ለ. ምስራቅና ምእራብ 9-10 ላይና ታች ባይደብቁኝ ንጋት በሚነጋበት በምስራቁ በኩል በማለዳ ተነስቼ ጸሐይ ሳትጠልቅ እንደ ንስር ሁለት ሜትር ክንፍ ባወጣና ወደ ምእራብ ብሸሽ ያ ይረዳኝ ይሆን? ለዚህ እንኳ ቀድመኸኝ መንገዱን ያበጀኸው አንተ ነህ –  በሁሉ ሥፍራ በአንድ ጊዜ ለሚገኘው ጌታ ምስራቅና ምእራብ የለውም ሁሉም ነገር ለእርሱ እዚህ ጋ ነው!!!!!  ስለዚህ ካንተ ሽሽት ከእግዜር ወጥቶ ወደ እግዜር መግባት ነው ካለ በኋላ – ከጅረት ወደ ወንዝ፣ ከወንዝ ወደ ሐይቅ፣ ከሐይቅ ወደ ባህር ከውሃ ወደ ውሃ

እግዚአብሔር በስፍራዎች ሁሉ ይገኛል ማለት ስፍራዎች ሁሉ እግዜር ናቸው ማለት አይደለም። እግዚአብሔር የመገኛዎቹም ድምር ውጤት አይደለም – ይኽ ፓንቴይዝም ነው እግዚአብሔር እዚህ እዛ ነው እንጂ እዚህ ውስጥ አይደለም። ለእግዜር የቀረበ ነጥብ ላይ ያለ ማንም የለም፣ ለዚህ ነው አማላጅ የሚባለው ነገር የማይሰራው” እንደታዋቂ ሰዎች አንተ ትቀርበዋለህ አናግርልኝ አይባልም። የስላሴ አካል እግዜር ሰው የሆነው ክርስቶስ ብቻ ነው ይህን ሚና የሚጫወት-  እግዚአብሔር ቁስ አይደለም በቅርበትና በርቀት ከ ጀምሮ እስከ አይባልም. “አለ” የሚለው ቃል የማይሰራበት የፍጥረቱ ክልል የለም። መዝ 139 ፡7-13

ስለዚህ፦ መንፈሳዊ ቦታ ነው ብለን ያልንበት ቦታ ስንገኝ የምናሳየው ጥንቃቄና ሌላው የህይወታችን ቦታ የምናሳየው አንድ ዐይነት ሊሆን ይገባል:: ይኼ እኮ ቤተ ክርስቲያን ነው እንዲህና እንዲህ አይባልም አይደረግም እንላለን እዚህ ያለው እዚያ የለም ወይ?